Site icon ethioelection.com

ቀጣዩ ምርጫ ነሐሴ 23 ይካሄዳል

ለምረጡኝ ዘመቻ ከግንቦት እሰከ ነሐሴ ያለው ጊዜ ተደልድሏል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ የካቲት 6 ይፋ አድርጓል። በይፋዊ የጊዜ ሰሌዳው መሰረት መራጮች ድምጽ የሚሰጡበት ቀን ነሐሴ 23 ቀን 2012 ይሆናል። ቦርዱ የተረጋገጠ ውጤት ይፋ የሚያደርገው ከምርጫው ማግስት አንስቶ እስከ ጳጉሜ 3 እንደሆነ አስታውቋል።

ምርጫ ቦርድ በጥር ባወጣው ረቂቅ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ላይ ቀጣዩ ምርጫ የሚካሄድበት ቀን ነሐሴ 10 እንዲሆን ሃሳብ አቅርቦ ነበር። በይፋዊ የጊዜ ሰሌዳ ላይ የድምጽ መስጫው በ13 ቀናት ወደፊት የተገፋ ሲሆን በሌሎች ክንውኖች ላይም ሽግሽግ ተደርጓል።

ከዚህ ቀደም በተካሄዱ አምስት ምርጫዎች የድምጽ መስጫ ቀናት የተደለደሉት ከሚያዝያ እስከ ነሐሴ ባሉት ወራት ውስጥ ነበር። ምስሉን ይመልከቱ። 

Exit mobile version